የምረቃ ስነስርአቱ በማርች ባንድና ሌሎች ክዋኔዎች ደምቆ እየተከናወነ ሲገኝ ሆስፒታሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዋና አማካሪና የአማካሪ ፅ/ቤት ኃላፊ(የርዕሰ መስተዳድሩ ተወካይ)
ዶ/ር ቦሼ ቦምቤ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ፣ የጋሞ ዞን ም/ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬና በጋራ ሪቫን ቆርጠው በይፋ መርቀዋል።
በፕርሮግራሙ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዋና አማካሪና የአማካሪ ፅ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ቦሼ ቦምቤ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩ፣ የጋሞ ዞን ም/አስተዳዳሪ ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬን ጨምሮ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።



